ZENA - LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures) http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC <p style="text-align: justify;">“ZENA LISSAN” is a bilingual, biannual and peer-reviewed journal which publishes original empirical studies, literature reviews, theoretical articles, methodological articles, book reviews, dissertation and thesis&nbsp;abstracts, synopsis of major research, short communications, commentaries, and other relevant issues in the area of languages and cultures.</p> en-US fikir2004@gmail.com (Fikre Gebrehiwot) Mon, 22 Apr 2019 06:50:35 +0000 OJS 3.1.2.1 http://blogs.law.harvard.edu/tech/rss 60 የቦረና ኦሮሞ የበኩር ልጅ ስም ስያሜ በዓል ክዋኔ አውድ http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1207 <p>ፎክሎር ህዝቦች በመኖሪያ አካባቢያቸውና በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች ሁሉ ሲገናኙ&nbsp;የሚከውኑዋቸው ወጎች፣ እምነቶች፣ ህዝባዊ ጥበቦችንና ሌሎችንም ያካትታል። ከነዚህ አንዱ<br>የሆነው የስም ስያሜ አንድ ህፃን ከነበረበት ደረጃ ወደ ተከታዩ ወይም ወደ ሌላ ደረጃ&nbsp;መሻገሩንና ወደ ማህበረሰቡ መቀላቀሉን ያመለክታል። ይህን መሰሉን የደረጃ ሽግግር<br>የሚያመለክተው ይህ ጥናት በኦሮሚያ ክልል፣ በቦረና ዞን በሚገኘው ቦረና ኦሮሞ የበኩር ልጅ&nbsp;ስም ስያሜ በዓል (ጉቢሳ) ላይ ያተኩራል። ቦረናን ጨምሮ የኦሮሞ ባህልና ወግ በአብዛኛው<br>ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የቆየው በቃል ነው፡፡ እነዚህ በቃል ያሉ አብዘኛዎቹ ባህልና&nbsp;ወጎች ወይም የፎክሎር ዘርፎች አልተጠኑም። በባህሪ ተለዋዋጭ በመሆናቸው በቃል<br>ሲያስተላልፉ የነበሩት የህዝቡ ባህላዊ፣ ማህበራዊና መንፈሳዊ እውቀቶችና እሴቶች፣ ይለወጣሉ፣&nbsp; ይረሳሉ፣ ይጠፋሉ። ስለዚህ አነዚህ አሁን በመከወን ያሉና የመለወጥ እድላቸው ሰፍቶ የሚታዩ<br>ባህላዊ ክዋኔዎች ተጠንተው በጽሑፍ ቢቀመጡ ነባሩን እውቀት ለትውልድ ማስተላለፍ ይቻላል።&nbsp;በመሆኑም ይህ ሀሳብ ለጥናቱ አነሳሽ ምክንያት ሆኗል። በጥናቱ የቦረና አሮሞዎች የበኩር ልጅ<br>ስም ስያሜ በዓል ሲያከብሩ ምንምን ክዋኔዎች ይከውናሉ? በየክዋኔዎቹ ምንምን የፎክሎር&nbsp;ዓይነቶች ይቀርባሉ ወይም ይካተታሉ? በየክዋኔዎቹ ውስጥ የህዝቡ ተሳትፎ ምን ይመስላል?<br>የሚሉት ጥያቄዎች ተመልሰዋል። የጥናቱ ዋና ዓላማ የቦረና ኦሮሞ ማንነትና አተያይ ማሳያ&nbsp;ከሆኑት የባህል ዘርፎች ውስጥ የበኩር ልጅ ስም ስያሜ በዓል ክዋኔዎች በውስጣቸው ከያዙት<br>የፎክሎር ዓይነቶች፣ ከሚኖራቸው ተምሳሌታዊ ፍችና ከሚያስተላልፉት መልዕክት አንፃር&nbsp;በመግለፅና በመተንተን መዝግቦ ማቆየት ነው፡፡ ይህን ዓላማ ለማሳካት በባህል እውቀታቸው<br>የላቁ ናቸው ተብለው ከሚታወቁት አባቶች ቁልፍ መረጃ አቀባዮች በታላሚ ናሙና ከተመረጡ&nbsp;በኋላ፣ (1)በቃለመጠይቅ (2) በምልከታ እና (3) ተሳትፎ ምልከታ ዘዴዎች መረጃዎቹ<br>ተሰብስበዋል። ፎክሎር በባህሪው ዘርፈ ብዙ የጥናት ክፍል በመሆኑ የተለያዩ የትንተና አንፃሮች&nbsp;በጥምር መጠቀም ይጠይቃል። ስለሆነም ለዚህ ጥናት መረጃዎች መተንተኛ በዋንኛነት<br>የተመረጡት የአውድና የክዋኔ የትንተና አንፃሮች ናቸው፡፡ በነዚህ የትንተና አንፃሮች በክዋኔዎች&nbsp;ሂደታዊ አፈፃፀም ባለጉዳዩ የመለየት፣ የሽግግር እና የመቀላቀል ደረጃዎችን ሲሻገር እንዲታይ፣<br>ክዋኔዎቹና በየክዋኔዎቹ የሚቀርቡት የፎክሎር ዓይነቶች ምንነትና ፍካሬያዊ ትርጓሜያቸውም&nbsp;እንዲሁ ጎልተው እንዲወጡ ተደርገዋል። ባጠቃላይ የበኩር ልጅ ስም ስያሜ በዓል ጉቢሣ<br>የተለያዩ የፎክሎር ዓይነቶች ማለትም ሥነቃል፣ ቁሳዊ ባህል፣ ሀገረሰባዊ ልማድና ትውን&nbsp;ጥበባትን አካቶ በመያዝ የቦረናን ኦሮሞ እምነት፣ አተያይ፣ ጠንካራ የርስ በርስ ግንኙነት፣ የምጣኔ<br>ሐብት አገነባብ ዘዴዎችና የባህል ህግጋት ጥበቃ ዘዴዎቹ ጎልተው እንዲታዩ ያደረገ በዓል ነው፡፡</p> ደስታ አማረ Copyright (c) 2019 ZENA - LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures) http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1207 Wed, 20 Jun 2018 00:00:00 +0000 በኢትዮጵያ የአራት ብሔራውያን ክልላውያን መንግሥታት የሕዝብ መዝሙሮች ይዘት ትንተና http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1208 <p>“የኢትዮጵያን ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የመሠረቱት” ብሔራውያን ክልላውያን መንግሥታት<br>በየሕገ መንግሥታቸው የየራሳቸው የሕዝብ መዝሙር እንደሚኖራቸውና በሕዝብ መዝሙሮቻቸው<br>ሊንፀባረቁ የሚገባቸውን ይዘቶች ደንግገዋል፡፡ ድንጋጌያቸውን ተግባራዊ በማድረግ የራሳቸው ክልል<br>ሕዝብ መዝሙር ያላቸው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ የዐማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣<br>የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ብቻ ናቸው፡፡ የዚኽ ጥናት<br>ትኩረትም በተጠቀሱት ብሔራውያን ክልላውያን መንግሥታት የሕዝብ መዝሙሮች ላይ ነው፡፡ ይኽን<br>ጥናት ማካኼድ ያስፈለገበት ምክንያት፣ በብሔራውያን ክልላውያን መንግሥታት የሕዝብ መዝሙሮች ላይ<br>የተደረገ ጥናት አለመኖርና ክፍተቱን ለመሙላት ምርምር ማድረግ አስፈላጊ በመኾኑ ነው፡፡ የጥናቱ ዐቢይ<br>ዓላማ የአራት ብሔራውያን ክልላውያን መንግሥታት የሕዝብ መዝሙሮች የሀገራችንን ታሪካዊ፣<br>ፖለቲካዊና ባህላዊ ኹኔታዎች ምን ያኽል እንዳንጸባረቁና በኅብረተ ሰቡ ውስጥ ለማስረጽ የተደረገውን<br>ጥረት መመርመርና ይዘቶቹን መተንተን ነው፡፡ ከዚኽ ዐቢይ ዓላማ የሚመነጩ ዝርዝር ዓላማዎችም፣<br>ብሔራውያን ክልላውያን መዝሙራቱን ለመድረስ ያነሣሡ ታሪካዊና ፖለቲካዊ ምክንያቶችን መመርመር፣<br>ብሔራውያን ክልላውያን መንግሥታት በየሕገ መንግሥታቸው ስለብሔራዊ ክልላቸው የሕዝብ መዝሙር<br>የደነገጓቸው ይዘቶች ምን ያኽል በየመዝሙሮቹ እንደተንጸባረቁ መመርመር፣ መተንተን፣ የሕዝብ<br>መዝሙሮቹ ብሔራዊ ማንነትን ለመገንባት (ለማጠናከር) (national identity building and<br>strengthening) እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን ለማጎልበልበት ያላቸውን ጠቀሜታ፣ ብሔራውያን<br>ክልላውያን የሕዝብ መዝሙራቱ ከፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር ጋር<br>እንዴት ተጣጥመው አገልግሎት እንደሚሰጡ መፈተሽና የሕዝብ መዝሙሮቹ የሚገልጹዋቸውን ርዕዮተ<br>ዓለሞች መመርመር የሚሉት ናቸው፡፡ እነዚኽን ዓላማዎች ለማሳካት ጥናቱ የሚመልሳቸው ጥያቄዎች፡-<br>ብሔራውያን ክልላውያን መዝሙሮቹን ለመድረስ ያነሣሡ ምክንያቶች ምን ምን ናቸው? ብሔራዊ ክልላዊ<br>መዝሙሮቹ የተደረሱበትን ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊና ማኅበራዊ እውነታ ምን ያኽል አንጸባርቀዋል?<br>በብሔራውያን ክልላውያን ሕገ መንግሥታት ስለሕዝብ መዝሙሮች የተደነገጉት ይዘቶች በሕዝብ<br>መዝሙሮቻቸው እንዴት ተንጸባረቁ? በብሔራውያን ክልላውያን የሕዝብ መዝሙሮች አማካይነት<br>በወጣቶች አዕምሮ እንዲሰርፁ የተደረጉትን ርዕዮተ ዓለሞች ብሔራዊና ሀገራዊ ጠቀሜታ ምን ያኽል ነው?<br>የሚሉት ናቸው፡፡ ጥናቱ፣ በተጠቀሱት ብሔራውያን ክልላውያን የሕዝብ መዝሙሮች ላይ ማተኰሩ<br>የተለያዩ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ የብሔራውያን ክልላውያን መዝሙራቱ ታሪክ ምን እንደሚመስል<br>ለመገንዘብ፣ የብሔራውያን ክልላውያን መዝሙራቱን ተግባርና አገልግሎት ለመረዳት በተለይም የብሔራዊ<br>ማንነትን ለመገንባት (national identity building and strengthening) ያላቸውን ሚና፣<br>(በብሔራውያን ክልላውያን የሕዝብ መዝሙሮች አማካይነት በወጣቶች አዕምሮ እንዲሰርፁ የተደረጉትን<br>ርዕዮተ ዓለሞች ለመረዳት ያስችላል፡፡) ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከርና ለማጎልበት ያላቸውን ጠቀሜታ፣<br>እንዲሁም ብሔራዊ ክልላዊ መዝሙራቱ ከፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኢትዮጵያ ብሔራዊ<br>መዝሙር ጋር እንዴት ተጣጥመው አገልግሎት እንደሚሰጡና በየሕገ መንግሥታቸው የሕዝብ<br>መዝሙሮቻቸው እንዲንጸባረቁ የተደነገጉት ይዘቶች እንዴት እንደተንጸባረቁ ለመረዳት ያስችላል፡፡<br>እንዲሁም፣ ወደ ፊት ለሚደረጉ ተመሳሳይ ጥናቶች መነሻነት ያገለግል፡፡ የዚኽ ጥናት የመረጃ ምንጮች<br>ጥናቱ ትኩረት ያደረገባቸው ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታት ሕገ መንንግሥቶች፣ የብሔራዊ ክልላዊ<br>መንግሥታት የሕዝብ መዝሙሮች፣ ዐዋጆች፣ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥቱን የሚመሩት</p> መስፍን መሰለ Copyright (c) 2019 ZENA - LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures) http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1208 Mon, 25 Jun 2018 00:00:00 +0000 የሃይማኖት መቻቻልን ማስተዋወቅ ለሰላማዊ አብሮነት በአርሲ ዞን ማሳያነት http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1209 <p>የጥናቱ ዋና አላማ፣ በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖት መካከል በሰላማዊ አብሮነት ለመኖር<br>ያስቻሏቸው የመቻቻል መገለጫ ፎክሎሮችን ማስተዋወቅ ይሆናል። ኢትዮጵያ በብሔረሰቦቹዋ<br>ውስጥና መካከል በታሪክ የተገነባው የብዝኀ-ባህል የግንኙነት መስተጋብር ባሕርያት ምን<br>እንደሚመስሉ ተጠንተው አልተገለፁም፡፡ አይታወቁም፡፡ የዚህ ጥናት ዋና ትኩረት በሆነው<br>በአርሲ ዞን፣ በሌሙና ቢልቢሎ ወረዳ ውስጥ የክርስትና እና የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ<br>ማህበረሰቦች መካከል ባለው የመቻቻል እሴት ከፎክሎር አንፃር ማሳየት ነው። በክርስትና እና<br>በእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች መካከል በሰላም ተከባብሮ ለመኖር ያስቻሏቸው የመቻቻል<br>ፎክሎር ምንድን ናቸው? በአርሲ ዞን በሌሙና ቢልቢሎ ወረዳ ለሰላማዊ አብሮነት<br>አስተዋጽዎ ያላቸው የመቻቻል ባህላዊ እሴቶች በተለይ እድር፣ ጡት መጣባትና ባህላዊ<br>እምነት ጥናቱ ያተኮረባቸው ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው። በማህበረሰቦች መካከል ያሉትን<br>የሃይማኖት ልዩነቶች በመቻቻል የሚመሩ፣ በባህል የተደነገጉና የተቁዋቁዋሙ ለዘላቂ ሰላም<br>መሠረትና ዋስትና ተግባራዊ ሕጎች ሆነው ይሠራሉ፡፡ ባህላዊ እሴቶቹ በተለይም በእስልምናና<br>በትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች መካከል ‘መቻቻል’ የሚለውን ፅንሰ-ሀሳብ፣<br>መርህና ተግብራዊ ድርጊቶች ማለትም፡- አንዱ የሌላውን ኅልውና ተቀብሎ እውቅና መስጠትን፣<br>መከባባርን፣ መተሳሰብን፣ መረዳዳትን፣ መተባበርን፣ አብሮነትን፣ አንድነትንና ሰላምን፣ ወዘተ፣<br>የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡</p> ፍሬህይወት ባዩ Copyright (c) 2019 ZENA - LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures) http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1209 Mon, 25 Jun 2018 00:00:00 +0000 Demonstratives in Silt’e http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1215 <p>This article intended to describe the system of demonstratives in Silt’e.<br>According to their distribution, forms and functions, demonstratives in<br>Silt’e categorize in to pronominal, adverbial and manner. Pronominal<br>demonstratives have two forms: free and complex. The free and complex<br>forms have two distinctions: proximal and distal. The free demonstrative<br>pronouns have neutral and focused form. The complex demonstrative<br>pronouns occur with preposition lə-, tə-and bə-, which indicate a dative,<br>ablative or comitative and instrumental or locative case of demonstrative<br>pronouns respectively. Adverbial demonstratives are formed by affixing<br>morphemes to basic demonstratives. Manner demonstratives are discourse<br>deictic, they formed by a combination of basic demonstrative pronoun and<br>simulative morpheme –ku, ‘like.’</p> Rawda Siraj Copyright (c) 2019 ZENA - LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures) http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1215 Mon, 25 Jun 2018 00:00:00 +0000 የደቂቀ እስጢፋኖስ ዐውደ ንባባዊ ትንታኔ http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1213 <p>የዚህ ጥናት ትኩረት ደቂቀ እስጢፋኖስ(“በህግ አምላክ”) በሚል ርዕስ በጌታቸው ሀይሌ ከግዕዝ<br>ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ለሁለተኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ፕሬስ የታተመ መጽሀፍ ነው።<br>የአባ እስጢፋኖስና የተከታዮቻቸው ገድል በጥቅሉ ደቂቀ እስጢፋኖስ ተብሎ አራት ገድሎችን<br>በአንድ ጥራዝ አካቶ ለህትመት በቅቷል። የጽሁፉ ዋና አላማ ደቂቀ እስጢፋኖስን በዐውደ ንባባዊ<br>ስልት መተንተን ይሆናል። በደቂቀ እስጢፋኖስ ገድል ውስጥ የተካተቱት ገድሎች የ15መ/ክ/ዘ<br>ኢትዮጵያዊያን በተለይም የሃይማኖት መጻህፍትን በማንበብ በመጻፍ እና በመመራመር የላቀ<br>አስተሳሰብ እንደነበራቸው የሚጠቁሙ ናቸው። አባ እስጢፋኖስ እና ተከታዮቻቸው ከአጼ<br>ይስሀቅ ጀምሮ እስከ አጼ ናኦድ ድረስ በነበረው ንትርክ ከደረሰባቸው መከራ ተነስተው<br>ገድላቸውን የጻፉት ተከታዮቻቸው ናቸው። በገድላቸው ውስጥ የምናየው በዘመኑ የነበረውን<br>የማሰብ ነጻነት ጠቋሚ አሻራዎች ነው። ይህም ጥናት በአውደ ንባባዊ ስልት ገድሉ ውስጥ የተነሱ<br>ኮዶችን በማፍታታት “ሀሳብን በሀሳብ እና ሀሳብን በስልጣን መርታት” የሚል አብይ ጭብጥ<br>ተለይቶ ወጥቶለታል። የአባ እስጢፋኖስና የተከታዮቻቸው ገድሎች እንደ ሌሎች ገድሎች ዐውደ<br>ንባቦቹ የሃይማኖት ናቸው። በአውደ ንባቦች ውስጥ ያሉት ድርጊቶች ሁነቶች እና ሁኔታዎች<br>ሃይማኖታዊ ናቸው። ሆኖም በእምነት አይን አይተን በእምነት ጆሮ ሰምተን በእምነት ልቡና<br>አምነን ይሁን ብለን የምናስተናግደው ብቻ አይደሉም። ስለዚህ ደቂቀ እስጢፋኖስ ከገድልነቱ እና<br>ከስነጽሁፍ ቅርስነቱ ባሻገር በተለያየ የሙያ መስክ ቢጠና፣ ማስረጃዎችን ለይቶ በማውጣት<br>ለሌሎች የጥናት መስኮች ግብአት በመሆን ያገለግላል።</p> ፍሬህይወት ባዩ Copyright (c) 2019 ZENA - LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures) http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1213 Mon, 25 Jun 2018 00:00:00 +0000 የሰቆጣ ወረዳ አለባበስና አጊያጌጥ ለውጥና ቀጣይነት http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1214 <p>የዚሀ ጥናት አላማ በቁሳዊ ባህል ስር የሚጠቀሰውን የሰቆጣ ወረዳን አለባበስና አጊያጌጥ ለውጥና<br>ቀጣይነት መግለጽ ነው፡፡ ጥናቴን በሰቆጣ ወረዳ ላይ እንዳከናወን ያነሳሳኝ ምክንያትም<br>በወረዳው አለባበስና አጊያጌጥ ላይ የተጠና ጥናት ባለመኖሩና በሉላዊነትና ‹‹በዘመናዊነት››<br>ምክንያት ሀገረሰባዊ አለባበሱና አጊያጌጡ እየቀነሰና በሌሎች ዘመናዊ አልባሳትና አጊያጌጥ<br>እየተተካ በመሄዱ፣ የማህበረሰቡ መገለጫነት ሊጠፋ ስለሚችል እንዲሰነድ ለማድረግ ነው፡፡<br>የጥናቱ ዘዴ ዓይነታዊ ሲሆን በመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያነት ያገለግሉትም ቃለ መጠይቅ፣<br>ምልከታ፣ ቡድን ተኮር ውይይትና ሰነድ ፍተሻ ናቸው፡፡ መረጃው የተሰበሰበው በመስክ ጉዞ ነው፡<br>፡ የጥናቱ ግኝት እንደሚያመለክተው ባህላዊ አለባበሱና አጊያጌጡ ባሁኑ ጊዜ ከሞላ ጎደል<br>የሚታየው በገጠር አካባቢ እንደሆነ ነው፤ ወደ ከተማ አካባቢ ግን ለውጡ ጎልቶ ይታያል፡፡<br>ስለሆነም ባህላዊ አለባበሱና አጊያጌጡ ገጽታውን ሳይለቅ እንዲቀጥል ማህበረሰቡና<br>የሚመለከታቸውው አካላት ለወጣቶች ማስተማርና ጠቀሜታውን መግለጽ ይጠበቅባቸዋል፡፡</p> አፀደ ተፈራ Copyright (c) 2019 ZENA - LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures) http://ejol.ethernet.edu.et/index.php/AELC/article/view/1214 Mon, 25 Jun 2018 00:00:00 +0000