Articles
የአመክሮ ሕጎችና አተገባበራቸው በባሕር ዳር ማረሚያ ቤት
- Journal Bahir Dar University Journal of Law
- Issue Vol 7 No 1 (2016): Bahir Dar University Journal of Law
- Published
- ISSN 2306-224X
Abstract
በኢትዮጵያ አመክሮ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው መልካም የሚባል የባሕርይ መሻሻል በማሳየታቸው 2/3ኛውን የእሥራት ጊዜ ካጠናቀቁ በኋላ ቀሪውን የፍርዱን 1/3ኛ ወይም በፍርድ ቤት የሚወሰነውን የሙከራ ጊዜ በአመክሮ ከእስር ተለቅቀው በሙከራ እንዲያሳልፉ የሚደረግበት አሰራር ነው፡፡1 ጥናቱ በተደረገበት በአማራ ብሄራዊ ክልል አንዱ በሆነው የባሕር ዳር ማረሚያ ቤትም ይኸው ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ ይሁን እንጂ በአመክሮ አተገባበርና ሕጉ ላይ ችግሮች ይስተዋላሉ፡፡ የዚህ ጥናት ዋና ዓላማም በክልሉ አመክሮ አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ የሕግ ክፍተቶችንና በማረሚያ ቤቱ አሉ የሚባሉ የአፈጻጸም ችግሮችን በመለየት የመፍትሄ ሐሳቦችን ለመጠቆም ነው፡፡ በማረሚያ ቤቱ የአመክሮ ሕጎችና አፈጻጸማቸው ምን እንደሚመስል በአይነታዊ የጥናት ዘዴ ለመመርምር ተሞክሯል፡፡ የጥናቱ መረጃዎችም በሳይንሳዊ መንገድ ተተንትነዋል፡፡ በዚህም መሰረት በወንጀል ሕጉና በአብክመ አመክሮ አሰጣጥ መመሪያ መካከል አለመጣጣምና የሕግና የአፈጻጸም ክፍተቶች መኖራቸውን የጥናቱ ግኝት አሳይቷል፡፡
Downloads
Download data is not yet available.