Articles
የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ሕግ የተፈፃሚነት ወሰን ከጊዜ አንፃር᎓- በፍርዶች ላይ የቀረበ ትችት
- Journal Bahir Dar University Journal of Law
- Issue Vol 4 No 2 (2014): Bahir Dar University Journal of Law
- Published
- ISSN 2306-224X
Abstract
ከፍትሐ ብሔር ሕጉ ድንጋጌዎች ጀምሮ በተለያዩ ጊዚያት በሀገራችን በርካታ የገጠር መሬት ሕጎች ታውጀዋል።1 እነዚህ ሕጎች በየዘመናቸው ለመሬት ባለቤቶች በኋላም ባለይዞታዎች የሚሰጡት መብት ወጥነት አልነበረውም፤ አሁንም የለውም፡፡2 ለምሳሌ በአዋጅ ቁጥር 89/1989 መሰረት የመሬት ባለይዞታው መሬቱን ለቤተሰብ አባሉ ብቻ ማውረስ እንደሚችል ተደንግጎ ነበር።3 በአማራ ክልል ከአዋጅ ቁጥር 46/1992 አንፃር ባለይዞታው መሬቱን በኑዛዜ የሚያስተላልፈው ለቤተሰብ አባሉ ወይም ለሚጦረው ሰው ብቻ ነበር፡፡4 በዚህ አዋጅ መሰረት መሬትን ያለ ኑዛዜ በውርስ ማስተላለፍ የሚቻለው ለባለይዞታው የቤተሰብ አባል ብቻ ነበር፡፡
Downloads
Download data is not yet available.