የሃይማኖት መቻቻልን ማስተዋወቅ ለሰላማዊ አብሮነት በአርሲ ዞን ማሳያነት

  • ፍሬህይወት ባዩ

Abstract

የጥናቱ ዋና አላማ፣ በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖት መካከል በሰላማዊ አብሮነት ለመኖር
ያስቻሏቸው የመቻቻል መገለጫ ፎክሎሮችን ማስተዋወቅ ይሆናል። ኢትዮጵያ በብሔረሰቦቹዋ
ውስጥና መካከል በታሪክ የተገነባው የብዝኀ-ባህል የግንኙነት መስተጋብር ባሕርያት ምን
እንደሚመስሉ ተጠንተው አልተገለፁም፡፡ አይታወቁም፡፡ የዚህ ጥናት ዋና ትኩረት በሆነው
በአርሲ ዞን፣ በሌሙና ቢልቢሎ ወረዳ ውስጥ የክርስትና እና የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ
ማህበረሰቦች መካከል ባለው የመቻቻል እሴት ከፎክሎር አንፃር ማሳየት ነው። በክርስትና እና
በእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች መካከል በሰላም ተከባብሮ ለመኖር ያስቻሏቸው የመቻቻል
ፎክሎር ምንድን ናቸው? በአርሲ ዞን በሌሙና ቢልቢሎ ወረዳ ለሰላማዊ አብሮነት
አስተዋጽዎ ያላቸው የመቻቻል ባህላዊ እሴቶች በተለይ እድር፣ ጡት መጣባትና ባህላዊ
እምነት ጥናቱ ያተኮረባቸው ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው። በማህበረሰቦች መካከል ያሉትን
የሃይማኖት ልዩነቶች በመቻቻል የሚመሩ፣ በባህል የተደነገጉና የተቁዋቁዋሙ ለዘላቂ ሰላም
መሠረትና ዋስትና ተግባራዊ ሕጎች ሆነው ይሠራሉ፡፡ ባህላዊ እሴቶቹ በተለይም በእስልምናና
በትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች መካከል ‘መቻቻል’ የሚለውን ፅንሰ-ሀሳብ፣
መርህና ተግብራዊ ድርጊቶች ማለትም፡- አንዱ የሌላውን ኅልውና ተቀብሎ እውቅና መስጠትን፣
መከባባርን፣ መተሳሰብን፣ መረዳዳትን፣ መተባበርን፣ አብሮነትን፣ አንድነትንና ሰላምን፣ ወዘተ፣
የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡

Downloads

Download data is not yet available.

References

ደስታ ተክለ ወልድ። 1962አዲስ የአማርኛ መዝገበ ቃላት፤ አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ።
የበቆጂ ከተማ ሁለተኛ ሸንጎ። 1988።“የመተዳደሪያ ውስጠ ደንብ(ያልታተመ)።
የሌሙና ቢልቢሎ ወረዳ አስተዳደር።2002።አጠቃላይ መረጃ።(ያልታተመ)።
Abbink, Jhon; 1998; An Historical-anthropological approach to Islam in Ethiopia:
Issues of identity and politics; Journal of African cultural studies,
Volume11, Leiden.
Abdullah, T. 2012. “Co-existence and Harmony in a pluralistic world: Gulen
movement as wording model,” a paper presented at a conference on
establishing and sustaining the culture of co-existence and mutual
understanding organized by ministry of Federal Affairs.
Braukamper, Ulrich. 1992; Religious Syncretism in Southern Ethiopia, Journal of
religion in Africa, Vol. 22, No. 3, pp. 194-207.
Federal Democratic Republic of Ethiopia, 2009; Central Statistical Agency; 2007
Population & Housing Census of Ethiopia; Addis Ababa.
Motz, Marilyn. 1998. The Practice of Belief, Journal of American Folklore
111:339-355,
Fetterman, D.M. 2009. Ethnography: Step-by-Step (3rded), New Deli, Saga
publication, inc.
Habermas, JÜrgen.2004.“Tolerance: The Pacemaker for Cultural Rights”,
Journal of Philosophy, vol. 79, No 30.
Mullen, B.; 2000; Belief and the American Folk. Journal of American
Folklore, 113(448):119-143.
Murphy, Andrew. 1997. “Toleration, and Liberal Tradition,”Journal of
Polity, vol. 29, No. 4, pp. 593-623.
Newman, Jay. 1978. “The Idea of Religious Tolerance”. Journal of American
Philosophical Quarterly,Vol. 15, No. 3, pp 87- 195.
UNESCO; 1995; Declaration of principles on Tolerance proclaimed and signed
by the Member States of UNESCO on 16 November 1995, Paris:
UNESCO.
Published
2018-06-25