የዐፄ ቴዎድሮስ ጀግንነት በአዝማሪ አንደበት

  • መስፍን መሰለ

Abstract

በኢትዮጵያ የአዝማሪና የቤተ መንግሥት ቅርርብ መቼ እንደ ተጀመረና ምን ሚና እንደ
ነበረው አይታወቅም፡፡ ይሁን እንጂ፣ ከጎንደር ዘመነ መንግሥት መጨረሻ ጀምሮ የአዝማሪንና
የቤተ መንግሥትን ቅርርብ በጥቂት የታሪክ ሰነዶች ተገልጾ እናገኛለን፡፡ አዝማሪ ጣፋጭ ከደጅ
አዝማች ጎሹ፤ አዝማሪ አብተው ከዐፄ ቴዎድሮስ፤ ሐሰን አማኑ መጀመሪያ ከዐፄ ዮሐንስ በኋላ
ከራስ (በኋላ ንጉሥ) ሚካኤል፤ ሊቀ መኳስ መርሻ ከራስ ኃይሉ፤ እሸቴ ጎቤ፣ ከራስ መኰንን፤
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ፣ ከልጅ ኢያሱ፤ ምስጋናው አዱኛ ከራስ ጉግሳ ወሌ፣ ወዘተረፈ ጋር የጠበቀ
ግንኙነት ነበራቸው፡፡ ከደጅ አዝማች ካሣ (በኋላ ዐፄ ቴዎድሮስ) ጋር የጠበቀ ቅርርብ የነበረው
አዝማሪ፣ በመሰንቆ ግርፍና ዜማ፣ በግብር፣ በዘመቻ፣ በክብረ በዓል፣ በሰርግ፣ በክርስትናና
በሌሎችም የተዝናኖት ጊዜያቶች፣ የጀግንነት ግጥሞችን እየደረደረ፣ ጌታውንና ታዳሚዎቹን
ያዝናናል፡፡ ያማረ ቀርቦ ግብር በሚበላበት፣ ጥሩ በሚጠጣበት ጊዜም፣ አዝማሪው የዘለሰኛና
የመዲና ግጥሞችን በማዜም በማዜም የታዳሚዎችን ስሜት ይቆጣጠራል፤ ያስደምማል፡፡ የሙገሳ
ግጥሞችን በመደርደር የታዳሚዎችን ቀልብ ወደ ተፈጸሙ ድርጊቶች በሐሳብ ይወስዳል፡፡
በሕይወት ያሉትንና የሌሉትን የጌታውን የቅርብ ዘመዶች፣ ጓደኞች እንዲሁም የራሱን ወዳጆች
ስምና መልካም ተግባራት እየዘረዘረ ያሞግሳል፤ ይዘክራል፡፡ የጌታውን ተቀናቃኞች በሌሉበት
ያኰስሳል፤ ይሰድባል፤ ይወቅሳል፡፡ ታዳሚዎቹም የአዝማሪው ሙገሳ እውነትነቱን ለማረጋገጥ
“እውነት እውነት ብለሃል” በማለት ምስክርነታቸውን ይሰጣሉ፡፡...

Downloads

Download data is not yet available.

References

ሊትማን፣ ኢኖ፡፡ ፲፱፻፪፡፡ የቴዎድሮስ ታሪክ ፡፡ ፕሪንስቶን፤ ሻርልስ ስክሪብኔር ልጆች፡፡
ሐረገወይን ሸዋረጋ፡፡ 2004፡፡ “በባህር ዳር ከተማ የታዋቂ አዝማሪዎች የህይወት ታሪክ እና ቃላዊ
ግጥሞች ክዋኔ፡፡” አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፤ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ-ጽሑፍ
ትምህርት ክፍል፣ የኤም.ኤ.ዲግሪ ማሟያ ጽሑፍ፡፡
መንገሻ አማረ፡፡ 1992፡፡ “የወገል ጤና አዝማሪዎች የሚጠቀሙባቸው ቃልግጥሞች፡፡” አዲስ
አበባ ዩኒቨርሲቲ፤ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ-ጽሑፍ ትምህርት ክፍል የመጀመሪያ
ዲግሪ ማሟያ ጽሑፍ፡፡
ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል፡፡ ፲፱፻፷፩፡፡ አማርኛ ቅኔ ከነ መፍቻው ተሻሽሎና ታክሎበት
የተሰናዳ፡፡ አዲስ አበባ፤ እሌኒ ማ. ኃ. የ. ግ. ማ.፡፡
ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል፡፡ ፲፱፻፷፩፡፡ ዝክረ ነገር ፡፡ አዲስ አበባ፤ ሴንተራል ማተሚያ
ቤት፡፡ .. more references are inside the pdf
Published
2017-12-30