የሁለት ደብዳቤዎች ንፅፅር

  • ባየ ይማም

Abstract

ይህ ጽሑፍ ዐፄ ቲዎድሮስና አባ እምነቱ የሚባሉ መነኩሴ የጻፏቸውን ደብዳቤዎች ያነጻጽራል፡፡ ንጽጽሩ የይዘትና የቅርጽ ነው፡፡ ቅርጹ ሥነ ልሳናዊ ሲሆን ይዘቱ ማኅበረ - ፖለቲካዊ፣ ባህላዊና ሥነ ልቦናዊ ነው፡፡ ጸሐፊዎቹ ሰበ-ሥልጣን ናቸው፡፡ አንዱ ዓለማዊ ንጉሠ ነገሥትና ኦርቶዶክሳዊ አማኝ፣ ሁለተኛው መንፈሳዊ መነኩሴና ከቶሊካዊ አማኝ፡፡ መነኩሴው የካቶሊክን እምነት ማስፋፋት፣ ዐፄው የኦርቶዶክስን እምነት መጠበቅ ይፈልጋሉ፡፡ ይህ በሁለቱ መካከል የሥልጣን ቅራኔ ይፈጥራል፡፡ ድብደቤዎቹ የተጻፉት በሁለቱ ጸሐፊዎች ጀርባ ለሚገኙ ሌሎች ሰበ- ሥልጣናት ነው፡፡ መነኩሴው ለፈረንሳይ፣ ዐፄው ለእንግሊዝ ወኪል የጻፏቸው የእርዳታ ጥሪ ናቸው፡፡ ጥሪው መልስ ያጣል፤ ስለዚህም ጭንቀት ይፈጠራል፡፡ ከዚህ የተነሣ ዐፄው በመነኩሴውና በደጋፊዎቻቸው ላይ እርምጃ የውስዳሉ፡፡ መነኩሴውን ያባርራሉ፤ ደጋፊያቸውን ይገድላሉ፡፡ ቅራኔው በግጭት ይቋጫል፤ ግን አይፈታም፣ እስከ ዐፄው ፍጻሜ ድረስ ይቀጥላል፡፡ የደብዳቤዎቹ ትንተና በይናዊ እና መራምራዊ ነው፡፡ ዓለማውም የቋንቋ ዓይነተኛ ተግባር ሥልጣንን መግለጽ መሆኑን ማሳየት ነው፡፡ የሁለቱ ሰበ-ሥልጣናት፣ የሁለቱ ቤተክርስቲያናት አልፎም የሁለቱ መንግሥታት (የኢትዮጵያና የፈረንሳይ) ግንኙት፣ ቅራኔና እርቅ፣ መሠረቱ ሥልጣን ነው፡፡ ቋንቋቸው ይህን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡ አልፎም ሃይማኖት የዓለማዊዉ ሥልጣን መጠበቂያና ማስጠበቂያ ከመሆን ያለፈ ፋይዳ እንደሌለው ያስረዳል፡፡ ቋንቋ የሐሳብ መግለጫ የሚሆነው ሐሳቡ ሥልጣን-አዘል ወይም ሥልጣን-አልባ ሲሆን ነው፡፡ ሥልጣን ዘርፉ እና ደረጃው ብዙ ነው፤ መግለጫው ቋንቋም እንደዚሁ ዓይነቱ ብዙ ነው፡፡ ሰምና ወርቅ አንዱ ነው፡፡

Downloads

Download data is not yet available.

References

Bahru Zewde. 2005. A History of Modern Ethiopia (1855-1991). 2 nd Edition. Addis Ababa:
Addis Ababa University
Brown, G and G. Yule. 1983. Discourse Analysis. Cambridge: Cambridge University Press
Dellboca, A. 1925. Thodore et Nouvel Empire D’Abyssinie. Roma
Levinson, S. 1983. Pragmatics. Cambridge: Cambridge University Press
Rubenson, S. (ed). Tewodros and His Contemporaries, 1855-1868. Addis Ababa: Addis Ababa University Press
Sperber, D. and D. Wilson.1986. Relevance Communication and Cognition. Oxford: Basil Blackwell
Tyler, S. 1978. The Said and the Unsaid: Mind, Meaning, and Culture. New York: Academic Press
ገብረ መድኅን እንዳለው፤ ቀን የሌለው፤ ወልደ አብ፣ አሳታሚ፡ ምስካበ ቅዱሳን ቆጋ ኪዳነ ምሕረት አፀደ ኤዎስጣቴዎስ አንድነት ገዳም
ተክለጻድቅ መኲሪያ፤ 1981፤ ዐፄ ቴዎድሮስና የኢትዮጵያ አንድነት ፣ አዲስ አባባ፡ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት
Published
2017-07-27