Articles

የቀብርና ሀዘን ሥርዓት ክዋኔዎች በወሊሶ ሊበን ኦሮሞ

Abstract

ይህ ጥናት በወሊሶ ሊበን ኦሮሞ የቀብርና የሀዘን ሥርዓት ላይ ያተኩራል። በጥናቱ አካባቢ ሞት
ከተከሰተበት ሰዓት ጀምሮ እስከ ሀዘኑ ፍፃሜ በባህሉ በተዋቀሩ ማህበራዊ ተቋሞች የሚከወኑ
ሥነርዓቶች አሉ። የእነዚህ በቅድመ ቀብር፣ በቀብርና ድህረቀብር የሚከወኑ ሥርዓቶችን የሚያሳዩ
መረጃዎች የተሰበሰቡት በቃለመጠይቅና በምልከታ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ሲሆኑ
መረጃዎቹ ከህይወት ዑደት የደረጃ ሽግግር አንፃር ተንትነዋል። በትንተናውም ሞተው በሚለዩና
ወደ “አያት ቅድመአያቶቻቸው በሚደመሩ” ወገኖች ሰበብ ህዝቡ ተሰባስቦ የሚከውናቸው
ድርጊቶች አብሮነቱን፣ መተጋገዙንና ፍቅሩን እንደሚያድስ ባህላዊ እሴቶቹን እንደሚጠብቅ
አጉልተው የሚያሳዩ መሆናቸውን መረዳት ተችሏል።

Downloads

Download data is not yet available.

Related articles